top of page

የወገናችንን ሕይወት መልሶ በማቋቋም እና ተስፋዉን በማደስ ከኢትዮጵያ ጎን እንቆማለን!

ተልዕኮ

ዝክረ ነዳያን ዘ አቡነ ኤልያስ ቀዳማዊ በኮሎራዶ የተመሰረተ ለትርፍ ያልተቋቋመ በሰው እና በተፈጥሮ ምክንያት የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያንን ለመርዳት የተደራጀ የበጎ አድራጎት ተቋም ነው። በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስዊድን እና የስካንዲኔቪያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የተመሰረተው ይህ ድርጅት በታለመላቸው መርሃ ግብሮች እና ፕሮጄክቶች አስፈላጊ የማዳን፣ የሰብአዊ እርዳታ እና የማገገሚያ አገልግሎት ይሰጣል። ከሌሎች መሰል የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ጋር በመተባበር እና ግልጽነትን በማረጋገጥ፣ የተቸገሩትን ለመደገፍ እና ለማንሳት፣ የወገናችንን ህይወት ለመለወጥ እና ብሩህ የወደፊት ተስፋን ለማጎልበት አላማ ያደርጋል።

2025 Fundraiser Event: Presented by Zikre Nedayan Ze Abune Elias I, Inc.

July 19,2025 Aurora, Colorado

Unite for Ethiopia: Ignite hope at Zikre Nedayan's Fundraising! Join His Grace Abune Elias, Archbishop of the Diocese of Sweden and Scandinavia, Member of the Holy Synod, alongside distinguished speakers in a memorable evening of inspiration. Be the spark that illuminates countless lives! Reserve your place now and join us in advancing our mission through the core values of kindness and support.

ለዝክረ ነዳያን የሚያደርጉት በጎ ልገሳ ለተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ጠቃሚ ግብአት፣ ድጋፍ እና ነጋቸው ብሩህ እንዲሆን ያደርጋል። እያንዳንዱ መዋጮ፣ መጠኑ ምንም ይሁን ምን፣ የመቋቋም አቅምን በመፍጠር እና ለተቸገረው ወገናችን ክብሩ ሳይነካ በሀገሩ ልጅ እምባዉ እንዲታበስ መንገድን ይፈጥራል። የበጎ ተልእኳችንን በመቀላቀል ፣ ተስፋ ወሰን የማያውቅበት አለም ለመፍጠር ዛሬዉኑ ይለግሱ።

በችግር ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ለመታደግ ከዝክረ ነዳያን ጋር አብረው ይስሩ። በተለያዩ ትርጉም በሚሰጡ መንገዶች በመሳተፍ ከፍተኛ ተፅእኖ መፍጠር ይችላሉ። ወራዊ አባል በመሆን፣ የተፈናቀሉ ወገንዎን ስፖንሰር በማድረግ፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመስጠት ወይም በድርጅት ስፖንሰርነት በመሳተፍ ተልእኳችንን ይደግፉ። እያንዳንዱ መንገድ ዘላቂ ለውጥ ለመፍጠር እና ተስፋን ለማለምለም እድል ይሰጣል። ተልእኳችንን ዛሬዉኑ ይቀላቀሉ።

ዝክረ ነዳያን በማያወላውል ቁርጠኝነት ህይወትን የሚቀይር በጎ አድራጎት፣ ሰብአዊ እርዳታ እና ለወገን ማገገሚያ የታለሙ ፕሮግራሞችን እና ፕሮጀክቶችን በመንደፍ ይተገብራል።
ከሌሎች ለትርፍ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር ጠንካራ ሽርክና በመፍጠር እና ከፍተኛውን የህግ እና ስነምግባር መመሪያ በዓፅንኦት በመከተል የገንዘብ ማሰባሰብ ስርዓትን በማክበር ተጽኖአችንን በማሳደግ የተልእኳችንን ዘላቂነትን እናረጋግጣለን።

bottom of page